Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13242 -
Telegram Group & Telegram Channel
#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።



tg-me.com/orthodox1/13242
Create:
Last Update:

#እለ_ኢፈለጡ_ፀጋሞሙ_እም_የማኖሙ
. (ግራቸውን ከቀኛቸው ያልለዩ) ☞ ዮና ፬፥፲፩

እንደምን አላችሁ? ለተቀረው ደግሞ ቅን በሆነ ቀን፣ በቀኝ ያውላችሁ!

በዚያን ወቅት የአሦራውያን ግዛትና የጤግሮስ ወንዝ መዳረሻ ሆና ስልምናሶር የሚያስተዳድራት ከአሥራሁለት እልፍ (መቶ ሃያ ሺህ) በላይ ሕዝብ እና ብዙ እንሰሳት ያሉባት ከተማ ነበረች፤ ይህች ከተማ ነነዌ ትባላለች፤

ቀድሞ ግን የሴም ልጅ አሦር የመሠረታት ከስልምናሶር በተጨማሪ ሰናክሬምና ሌሎችም ነገሥታት ያስተዳደሯት ለአሦራውያን ግዛት መዲና ሆና የኖረችው ጥንታዊቷ ‘እመ አህጉር’ ዛሬ በባግዳድ አንፃር በሰሜን ኢራቅ የምትገኝ “ታላቅ” ከተማ ናት ፦ ይኽችው ነነዌ።

እግዚአብሔር የአማቴ እና የሶና ልጅ የሆነውን ነቢዩ ዮናስን ስለሕዝቡ ክፋት የከተማዋን በሦስት ቀን መጥፋት ‘እንዲሰብክላቸው’ ቢልከውም እርሱ ግን ከተርሴስ ወደብ ተነስቶ ወደ ኢዮጴ በሚሔድ መርከብ መሸሽን መረጠ፤ የታዘዘ ዓሣ አንበሪ (አሳነባሪ) ግን በተኣምራት ዮናስን ከአንቀጸ ነነዌ (ወደ ነነዌ መግቢያ) በሦስት ቀን አደረሰው … "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታዕ ነነዌ" እያለ አስተማረ፤

ያን ጊዜ ልጅ ከእናት ላም ከጥጃ እንዳይገናኙ ከብቶቻቸውም ሳር እንዳይነጩ ውኃ እንዳይጎነጩ እንዳይሰማሩ ጭምር የአዋጅ ጾም አዘዘ በንስሐ በጾም የ፫ ቀን ‘ሱባዔ’ ወደ ፈጣሪያቸው ተመለሱ እንሰሳቱም ሳይቀር ተባበሩ እግዚአብሔርም አዘነላቸው፤ ቀድሞውኑ ዮናስም ይኼን ነበር ‘የፈራው’
⇢ አንተ በመሐሪነትህ እንድትመለስ የሕዝቡ ንስሐ (ጸጸት) እንድትጸጸትም ያደርግሃል "ወነስሐ በከመ ብዝኀ ምሕረቱ … እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ " እንዲል (መዝ ፻፭፥፵፭) እኔንም ነቢየ ሀሰት አስባልከኝ፤ ብሎ እሳት ባለመውረዱ አዝኖ ከከተማው በአፍአ (ውጪ) ጎጆ ሰርቶ ተቀመጠ በአንድ ሌሊት የበቀለች ቅል ዋዕየ ፀሐዩን ትከለክልለታለች፤ ይኼኔ በደስታ ከጥላው ሥር ተኝቶ ሳለ የታዘዘ ትል ቆርጦ ቅሊቱን ጣላት ደረቀችም … ያኔ ዋዕየ ፀሐይ (የፀሐዩ ንዳድ) ራሱን ቢመታው "አዳጊት" (ራስምታት) ተነሳችበት አዘነ፤ ‘እግዜሩም’ ⇒ ላልተከልካት፣ ባዛ ላይ ውሃ እንኳ አጠጥተህ ላልደከምክባት ሌሊት በቅላ ሌሊቱን ለደረቀች አንዲት ቅል አንተ ካዘንክ ↳
"ወአንሰ ፡ ኢይምሕካ ፡ ለነነዌ ፡ ሀገር ፡ ዐቢይ ፡ ዘሀለወ ፡ ውስቴታ ፡ ሰብእ ፡ ፈድፋደ ፡ እምዐሠርቱ ፡ ወክልኤቱ ፡ እልፍ ፡ እለ ፡ ኢፈለጡ ፡ ፀጋሞሙ ፡ እምየማኖሙ ፡ ወእንስሳ ፡ ብዙኅ … እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? አለው።" (ዮና ፬፥፲፩)

በትንቢተ ዮናስ የመጨረሻ ምዕራፍና የመጨረሻ ቁጥር ላይ የምናገኘው የዐረፍተ ነገሩ ሐረግ ፦
⇝ እለ ኢፈለጡ ፀጋሞሙ እምየማኖሙ (ቀኛቸውን ከግራቸውን ያልለዩ) የሚል ነው፤ ይኽ አገባብ ነነዌን ለጥፋት የዳረጋት ከእንሰሳቱ ጋር ያስቆጠራት ልክ እንደ እንሰሳቱ ግራና ቀኝ አለመለየት ነበርና፤ በአንድ ላይ ሰዉን ከእንሰሳው ጋር ግራና ቀኝ ስለማይለዩ ሊያጠፋቸው ብሎ ዮናስን ላከ… ነገር ግን የነነዌ ሰዎች ይኽን ሰምተው "በእግዚአብሔር አመኑ" (፫፥፭) ያኔ ከግራቸው ላይ ቀኛቸውን ለዩ ወደሚያድናቸው አምላክ ጸለዩ። በርቱዕ ምግባር በጾም ለቅን ሥራ አደሩ በቀኝም ዋሉ!

#ቀኝ (የማን) እና #ግራ (ፀጋም) ምንድነው ?
. ┈┈┈◦◎ ⇆⇡⇄ ◎◦┈┈┈

በቁሙ የማን ፦ ቀኝ፣ የቀኝ እጅ፣ የቀኝ ጐን እንዲሁም ፀጋም ፦ የቀኝ አንጻር፣ የግራ እጅ፣ የግራ ጐን በሚል አቅጣጫ የሚጠቆምበት ነው፤ በዘይቤው ግን በጎውን ከክፉ መልካሙን ከመጥፎ ለይተን የምናመለክትበትም መገለጫ ነው!

የሚን ፦ መቅናት ቅን ቀኝ መኾን፣ መጽናት (መበርደድ) ፣ መብዛት (መፈድፈድ) ፣ መክበር (መወደድ) ፣ በቀኝ መቀጥቀጥ ወደ ቀኝ መኼድ ማለትን ይወክላል።

ፀጊም ፦ መጥመም መጕበጥ ጠማማ መኾን ወደ ግራ መኼድ መገልበጥ ማለት ነው ። ከዚህም በመነሳት ፀጋም ወይም ግራ ሀካይ ድኩም የሚለውን ተክቷል።

መጽሐፍም ጥበብና ስንፍናን ፣ ብርታትና ድክመትን ፣ ቅንነትና ጥመትን… ቀኝና ግራ እያለ ይገልጣል፤
↦ "ልበ ጠቢብ ውስተ የማኑ ወልቡ ለአብድ ውስተ ፀጋሙ … የጠቢብ ልብ በስተ ቀኙ ነው፥ የሰነፍ ልብ ግን በስተ ግራው ነው።" እንዲል (መክ ፲፥፪) ይኽንኑ ለማጉላት በተለየ አተያይም #ሀይመነ የሚለው የሃይማኖት መነሻ አመነ ታመነ ማለት ሲሆን ንባቡ #ከየማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው ይሉናል ሊቃውንቱ።

‘እግዜሩም’ ጥንቱን አክብሮ በአምሳያው ሰውን ሲፈጥረው በእውቀትና በሕይወት በዚያ ውም ላይ በነጻ ፈቃድ ከሌላው የከበረ አድርጎታል። ግራና ቀኙን የሚለይበትን እውቀት ከነጻ ፈቃድ ጋር አድሎታል ፤ ይሁንና «እንዳሻኝ» ብሎ አምላኩን በድሎ ከክብር እንዳይርቅ ከማዕረጉ እንዳይወድቅ «ቀኝ ከግራ እያወላወለ በመንታ እንዳይቅበዘበዝ በግራው ድካም ጠፍቶም እንዳይቀር» በምትሻው ለመሔድ ፈቃድ አለህ ግን የሚጠቅምህ ቀኙ ነው እያለ መልካሙን ያመለክተዋል፣ የሚጠቀምበትን ይነግረዋል።

" ወኢትትገኀስ ኢለየማን ወኢለፀጋም በከመ አዘዘ ሙሴ ለደቂቀ እስራኤል። አቅረብኩ ለከ እሳተ ወማየ ኀበ ዘፈቀድከ ደይ እዴከ። ☞ እሳትንና ውኃን አቀረብኩልህ፤ እጅህን ወደ ወደድኸው ጨምር ብሎ ሙሴ የእስራኤልን ልጆች እንዳዘዛቸው ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ አትበል" [፩. መቃ ፯፥፯]

ተጨማሪ ምክርም መቃቢያኑ አክለዋል እንዲህ ሲሉ " ቃሉን ትሰማ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ታደርግ ዘንድ የምነግርህን ቃሉን ስማ፤ በባሕር ማዶ፥ ወይም በጥልቁ ማዶ፥ ወይም በወንዙ ማዶ ቃሉ አለች፤ አያት ዘንድ፥ ቃሉንም እሰማ ዘንድ፥ የእግዚአብሔርንም  ትእዛዙን አደርግ ዘንድ ማን ያመጣልኛል? እንዳትል፥  ዳግመኛም ሰምቼ አደርጋት ዘንድ ወደ ሰማይ ወጥቶ ያቺን የእግዚአብሔርን ቃል ማን ያወርድልኛል? እንዳትል እነሆ ቃሉ በአፍህ ቅርብ ነው። በእጅህም ውስጥ ነው።  መጽሐፉንም ካልሰማኸው አምላክህ እግዚአብሔርን  አልሰማኸውም፤ ቃሉንም ካልጠበቅህ እርሱን አልወደድኸውም፤ ትእዛዙንም አላደረግህም። አንተም ትእዛዙን ካልወደድህ በእውነትም ትጠብቃቸው ዘንድ ከወገኖችህ ሁሉ ለይቶ ያከበረህንና ያገነነህን ፈቃድ ካላደረግህ ለዘለዓለም ወደ ፍርድ ትገባለህ።"

እሳት ከውኃ ለይተን ቀኛችንን ከግራችን አንስተን እንደቃሉ ኖረን ለመክበር ያብቃን!

ከዚህ ዘይቤ በበለጠው ምሥጢር ደግሞ ቅዱስ መጽሐፍ ግራ እና ቀኝ በሚለው ሰሜንና ደቡብን ፣ ጌባልና ገሪዛንን ፣ ዳክርስ እና ጥጦስን፣ ፍየልና በግን… ይህን የመሰለውን ሁሉ እያስተያየ የሚገልጥ አስተማሪ ቃል ነው፤

① #ሰሜን እና #ደቡብ (ሰሜን የግራ ደቡብ የቀኝ አቅጣጫ )
. ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈

ከአራቱ ዐበይት ማእዘንት ምዕራብ እና ምሥራቅ ውጪ ያሉትን ሰሜንና ደቡብ እንላቸዋለን፤ ገጻችንን(ፊታችንን) ወደ ሥርቀተ ፀሐይ ምሥራቅ (ወደ ፀሐይ መውጫ) አዙረን እጆቻችንን ስንዘረጋ በቀኝ አቅጣጫ ደቡብን በግራ ደግሞ ሰሜንን እናገኛለን ከዚኽ በመነሳት ሰሜን ግራ ደቡብ ቀኝ ተሰኝቷል ይህም ከቀኙ ደቡብ ከግራው ሰሜኑ ተገምቷልና።

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13242

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The STAR Market, as is implied by the name, is heavily geared toward smaller innovative tech companies, in particular those engaged in strategically important fields, such as biopharmaceuticals, 5G technology, semiconductors, and new energy. The STAR Market currently has 340 listed securities. The STAR Market is seen as important for China’s high-tech and emerging industries, providing a space for smaller companies to raise capital in China. This is especially significant for technology companies that may be viewed with suspicion on overseas stock exchanges.

Should You Buy Bitcoin?

In general, many financial experts support their clients’ desire to buy cryptocurrency, but they don’t recommend it unless clients express interest. “The biggest concern for us is if someone wants to invest in crypto and the investment they choose doesn’t do well, and then all of a sudden they can’t send their kids to college,” says Ian Harvey, a certified financial planner (CFP) in New York City. “Then it wasn’t worth the risk.” The speculative nature of cryptocurrency leads some planners to recommend it for clients’ “side” investments. “Some call it a Vegas account,” says Scott Hammel, a CFP in Dallas. “Let’s keep this away from our real long-term perspective, make sure it doesn’t become too large a portion of your portfolio.” In a very real sense, Bitcoin is like a single stock, and advisors wouldn’t recommend putting a sizable part of your portfolio into any one company. At most, planners suggest putting no more than 1% to 10% into Bitcoin if you’re passionate about it. “If it was one stock, you would never allocate any significant portion of your portfolio to it,” Hammel says.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from ru


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA